ኮሚሽኑ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ከ97 ቢሊዮን ብር በላይ ሰብስቧል፡፡ “በአህጉር ደረጃ የተሰጠን እውቅናና ሽልማት በየደረጃው የሚገኙ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮች እና ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት እና ባስመዘገቡት ድምር ውጤት የተገኘ ነው” ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር

Resultats de la cerca

Aplicacions anidades

Publicador de continguts

null “በአህጉር ደረጃ የተሰጠን እውቅናና ሽልማት በየደረጃው የሚገኙ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮች እና ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት እና ባስመዘገቡት ድምር ውጤት የተገኘ ነው” ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር

የአፍሪካ ምርጥ የመንግስታዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሽልማት አዘጋጅ ድርጅት አማካኝነት በተዘጋጀው አህጉር አቀፍ ልዩ ሽልማት “ምርጥ የአፍሪካ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር” ሆነው እውቅና ያገኙት የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ፤ ወደቢሯቸው ሲመለሱ የኮሚሽኑ ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

በተዘጋጀው  መርሀግብር ማጠቃለያ ላይ ንግግር ያደረጉት ኮሚሽነር ደበሌ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን የነበረበትን ውስብስብ ችግሮች በመቅረፍ  ባለፉት አራት ዓመታት  ህዝብን እና ሀገርን ተጠቃሚ ያደረጉ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን አስረድተዋል፡፡

እነዚህ ስኬቶች የመጡት በምኞት ሳይሆን ጠንክሮ በመስራት የተገኙ ውጤቶች መሆናቸውን ያስታወሱት ኮሚሽነር ደበሌ፣ ኮሚሽኑ በቀጣይም  ሁለንተናዊ ለውጥ ማምጣት የሚያስችሉ ስራዎች ላይ  ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ጠቅሰዋል፡፡

“በሀገር  እና በአህጉር አቀፍ ደረጃ እየተሰጡን ያሉት ሽልማቶች ጉምሩክ ኮሚሽን በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኑን ማሳያ ናቸው” ያሉት ኮሚሽነሩ  ሰሞኑን የተገኘው  እውቅናና ሽልማት በየደረጃው የሚገኙ የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮች  እና ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት እና ባስመዘገቡት ድምር  ውጤት የመጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከእውቅናና ሽልማት ባሻገር የጉምሩክ ኮሚሽን መላው ኢትዮጵያዊያን የሚኮሩበት እና እምነት የሚጥሉበት ጠንካራ የህዝብ ተቋም እንዲሆን ብርቱ ጥረት ይደረጋልም ብለዋል፡፡

የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በበኩላቸው የተሰጠው እውቅናና ሽልማት በህዝብ እና በመንግስት የተሰጣቸውን ኃላፊነት  በላቀ ደረጃ ለመወጣት ተጨማሪ አቅም እንደሚሆናቸው አስረድተዋል፡፡

በመጨረሻም የኮሚሽኑ አመራሮች እና ሰራተኞች በጋና ዋና ከተማ አክራ “ምርጥ የአፍሪካ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር” ሆነው እውቅና ላገኙት  ለኮሚሽነር  ደበሌ ቃበታ ፣ ስጦታ አበርክተውላቸዋል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission

 

 

Publicador de continguts

Publicador de continguts

null ኮሚሽኑ በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ከ97 ቢሊዮን ብር በላይ ሰብስቧል፡፡

(ጉምሩክ ኮሚሽን፣ የካቲት 2 ቀን 2016 ዓ.ም)

የጉምሩክ ኮሚሽን የ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በዚህ የግምገማ መድረክ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወራት ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰው በገቢ አሰባሰቡ የተመዘገበው ውጤትም ስኬታማ እንደነበር አስረድተዋል፡፡

በ2016 የመጀመሪያው ግማሽ የበጀት ዓመት ከተለያዩ የገቢ አርእስቶች 103 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ እቅድ የነበረ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ  97 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡንም ገልፀዋል፡፡

ገቢው የተሰበሰበው ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስ እና ከሌሎች ታክስ እና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ነው ያሉት ኮሚሽነር ደበሌ ካለፈው የበጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀርም በ9.9 ቢሊዮን ብር (11.42 በመቶ) ብልጫ ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡
የኮሚሽኑ የስትራቴጂክ ፕላን እና ፕሮጀክት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብዲሳ ዱፌራ የኮሚሽኑን የ2016 ግማሽ በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበው ውይይት እየተደረገበት ይገኛል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopianCustomsCommission

Untitled Basic Web Content

የእኛ አገልግሎቶች

 

 

 

 

Publicador de continguts

Aplicacions anidades

Publicador de continguts

ጠቃሚ መረጃዎች