Asset Publisher

null ግብር ለሀገር ክብር በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነት ንቅናቄ የታክስ መሰረትን ለማስፋት፣ የአሰራር ስርዓትን ምቹ ለማድረግ ብሎም የህግ ተገዥነት ዓቅምን ለማሳደግ ይረዳልߴߴ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ

ግብር ለሀገር ክብርߴߴ በሚል መሪ ቃል የካቲት 23/2015 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የተጀመረው ሀገራዊ የታክስ እና የጉምሩክ የህግ ተገዥነትን ንቅናቄ  በተለያዩ ሁነቶች መከበሩን እንደቀጠለ ይገኛል፡፡

የዚሁ የንቅናቄ  አካል የሆነው የንቅናቄ መድረክ ߵߵእኔ ታማኝ አገልጋይ ነኝ ߴߴበሚል መሪ ሀሳብ የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ፣ የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ የጉምሩክ እና የገቢዎች ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ፣ ሰራተኞች ፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራአስኪያጆች እና የታክስ እና የጉምሩክ አምባሳደሮች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው፡፡

 በንቅናቄው መድረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት  የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ የሀገርን ህልውና በአስተማማኝ መሰረት ለማስቀመጥ የጠንካራ መንግስታዊ ተቋም መኖር አስፈላጊ  መሆኑን ጠቅሰው ይህን እውን ለማድረግም ባለፉት አራት አመታት በርካታ የሪፎርም ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል፡፡

ተግባራዊ ከተደረጉት  የለውጥ ስራዎች መካከልም  የህግ፣ የአሰራር ለውጦች፣ የቴክኖሎጂ ማሻሻያዎች እና  የህግ ተገዥነት ሪፎርሞች በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው ያሉት ኮሚሽነር ደበሌ እነዚህን ሪፎርሞች ተግባራዊ ሲደረጉም  በርካታ መስዋእትነቶች  እንደተከፈሉም ገልጸዋል፡፡

ኮሚሽነር ደበሌ አክለውም ፤ እነዚህን የለውጥ ስራዎች የሚገዳደሩ እና ሀገር ከጀመረችው የብልጽግና ትልም ተቃራኒ የሆኑ  የተለያዩ መሰናክሎች እያጋጠሙ እንደሆነ ተናግው ደበሌ  እነዚህን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት የጉምሩክ እና የገቢ ተቋማትን ማጠናከር እና ማዘመን ብሎም አስተማማኝ ገቢ መሰብሰብ ወሳኝ  ነው፡፡

ግብር ለሀገር ክብር በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የታክስ እና የጉምሩክ ህግ ተገዥነት ንቅናቄም የታክስ መሰረትን ለማስፋት፣ ግንዛቤን ለማሳደግ ፣ የአሰራር ስርዓትን ምቹ ለማድረግ በአጠቃላይ የህግ ተገዥነትን ዓቅምን ለማሳደግ ይረዳልም ብለዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽንን የተመለከቱ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ecczena
በድረ ገጽ፦ www.ecc.gov.et
በቴሌግራም፦ https://t.me/EthiopiaCustomsCommission